16/08/2024
አሸንድዬ፣ እንግጫ ነቀላ እና ከሴ አጨዳ ከነሃሴ አጋማሽ ጀምሮ በጎጃም ይከበራሉ። እንግጫ የሳር አይነት ነው። የእንግጫ ነቀላ በዓል ደግሞ ዘመን ሲለወጥ የሚከወን ባህላዊ ስራት ነው። በአዲስ አመት ዋዜማ ልጃገረዶች ወንዝ ወርደው እንግጫ ይቆርጣሉ። በዚያዉ ቀን ማምሻ የቆረጡትን እንግጫ ይጎነጉኑታል። ሲነጋ ሊጃገረዶቹ ከያሉበት ተጠራርተው በመሰባሰብ በየሰው ቤት እየዞሩ የተጎነጎነውን እንግጫ የቤቱ ምሰሶ ላይ በማሰር አዲሱን አመት ያበስራሉ። ይህ ባህላዊ ክዋኔ በዜማና በጭፈራ የታጀበ ነው።