National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia

National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia, Addis Abeba.

Who Are NCLACE ❓

🎯Legally registered national coalition (July 2024)

🎯Founded by 3 care leaver-led associations:-

1️⃣.Selam Fruits Association

2️⃣.The Prev.SOS Children's Village's Youth Association Ethiopia

3️⃣.4Care Leavers Association

15/06/2026
ስፖርት ለጤና፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ መተኪያ የሌለው አሻራ! 🌱⚽በትላንትናው ዕለት በደመቀ ሁኔታ በተጠናቀቀው የመጀመሪያው የኬር ሊቨርስ ማህበራት ስፖርት ፌስቲቫል (Care Leavers As...
15/06/2026

ስፖርት ለጤና፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ መተኪያ የሌለው አሻራ! 🌱⚽

በትላንትናው ዕለት በደመቀ ሁኔታ በተጠናቀቀው የመጀመሪያው የኬር ሊቨርስ ማህበራት ስፖርት ፌስቲቫል (Care Leavers Associations Sport Festival) ላይ ከአስደሳቹ የስፖርት ውድድር ጎን ለጎን፣ የ2026 የዓለም የአካባቢ ጥበቃ ቀንን (World Environment Day) በማስመልከት ልዩ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ኤስ ኦ ኤስ የሕፃናት መንደር በድምቀት ተካሂዷል።

! በሚል መሪ ቃል በተከናወነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ የወጣቶች ማህበራት አመራሮች፣ የሚዲያ አካላት እና በርካታ ወጣቶች በተግባር በመገኘት የአካባቢ ጥበቃ መልዕክታቸውን አሻራቸውን በማሳረፍ አስተላልፈዋል።

የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ እና ለወጣቶቻችን ያለው ፋይዳ👇

✅️ ሁለንተናዊ ዜጋን ለመገንባት ወጣቱ በስፖርት አካሉንና አእምሮውን እንደሚያጠናክረው ሁሉ፣ ለተፈጥሮና ለሀገር ደህንነትም የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ማድረግ የነገ ሀገር ተረካቢነቱን በተሟላ መልኩ ያረጋግጣል።

✅️ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የአየር ንብረት መዛባት የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ለመቀነስና ለአካባቢያችን ዘላቂ ጥበቃ ለማድረግ የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ ሚና አለው።

✅️ የማህበረሰብ ትስስር እንዲሁም የስራ እድል ፈጠራ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ወጣቶች በአንድነት እንዲሰሩ ከማድረጋቸውም በላይ፣ ወደፊት ከከተማ ግብርና እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ጋር በተያያዘ ሰፊ የስራ እድሎችን የመፍጠር አቅም አለው።

👉 የብሔራዊ ኬር ሊቨርስ ማህበራት ጥምረት ኢትዮጵያ National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) ይህንን የአረንጓዴ ልማት ስራ በስትራቴጂካዊ እቅዱ ውስጥ አካቶ የገዛው ሲሆን፣ ወደፊትም አባል ማህበራትን በማስተባበርና በማንቀሳቀስ ይበልጥ ሰፊና ተከታታይነት ያላቸውን የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ለመምራት ቁርጠኛ ነው።

ወጣቶቻችን በስፖርታዊ እንቅስቃሴው ያሳዩትን ከፍተኛ ተነሳሽነትና ጉልበት፣ ለሀገራዊ የአረንጓዴ ልማት ጥሪም በተግባር በመመለስ አርአያነታቸውን አሳይተዋል!

የሁላችንም አረንጓዴ አሻራ ለተሻለችና ለለመለመች ነገ! 🌍💚

# # # # # # # # # # # # # # # # # # # # #

Sports for Health, Green Development for a Sustainable Tomorrow! 🌱⚽

Alongside the thrilling athletic competitions at yesterday's closing of the 1st Care Leavers Associations Sport Festival, a special tree-planting initiative was successfully held at the SOS Children’s Villages compound in Addis Ababa, in commemoration of World Environment Day 2026.

Guided by the inspiring motto, "One Sapling for Tomorrow, One Mark for Nature," youth participants, association leaders, distinguished guests, and media representatives stood together to leave their green legacy and amplify the call for environmental conservation.

The Significance of Green Development for Care Leavers & Youth:👇

♻️ Fostering Holistic Citizenship: Just as sports strengthen the mind and body, engaging in environmental stewardship empowers young people to take active responsibility for their country’s future.

♻️ Combating Climate Change: Active youth climate resilience, reducing ecological degradation, and securing a sustainable environment.

♻️ Community Integration & Green Jobs: Beyond environmental protection, green initiatives foster deep community solidarity and open doors for future economic opportunities through urban agriculture and eco-friendly entrepreneurship.

The National Care Leavers Association Coalition Ethiopia (NCLACE) has institutionalized green development as a core pillar of its strategic plan. Moving forward, the Coalition is fully committed to mobilizing its member associations across the nation to lead larger, structured, and impactful environmental initiatives.

Our youth have powerfully demonstrated that the same energy and passion driving them on the sports field can be channeled to spearhead national green legacy efforts.

Let us all leave our mark for a greener, brighter tomorrow! 🌍💚



SOS Children's Villages in Ethiopia SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa Embassy of Denmark in Ethiopia SOS Børnebyerne SOS Children's Villages International የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association SELAM Fruits Association African Union

ታሪካዊው የመጀመሪያው የ Care Leavers Associations Sport Festival በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ!🔥✅️ላለፉት ሁለት ሳምንታት በታላቅ ጉጉት እና እልህ አስጨራሽ ፉክክር ሲካ...
14/06/2026

ታሪካዊው የመጀመሪያው የ Care Leavers Associations Sport Festival በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ!🔥

✅️ላለፉት ሁለት ሳምንታት በታላቅ ጉጉት እና እልህ አስጨራሽ ፉክክር ሲካሄድ የቆየው፣ በ National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የ Care Leavers Associations Sport Festival ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ዛሬ እሁድ ዕለት እጅግ በደመቀ እና ባማረ መልኩ ፍጻሜውን አግኝቷል።

📍ይህ ስፖርታዊ ውድድር ከማሸነፍ እና ከመሸነፍ በላይ ትርጉሙ እጅግ ግዙፍ ነው። ጥምረቱ (NCLACE) ይህንን ታሪካዊ መድረክ ሲያዘጋጅ ያስቀመጣቸው ዋና ዋና ዓላማዎች ሙሉ ለሙሉ ተሳክተዋል። እነዚህም ዓላማዎች ባጭሩ ሲቀመጡ👇

👉 አንድነትን እና ትስስርን ማጠናከር ከአማራጭ እንክብካቤ እና ድጋፍ መስጫ ተቋም ላይ አድገው የወጡ ወጣቶች የመሰረቶቸው ማህበራት መካከል ያለውን ወንድማማችነት እህትማማችነት እና ትብብር ማጎልበት።

👉የወጣቶቹን አቅም፣ ስፖርታዊ ክህሎት እና በህብረተሰቡ ውስጥ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ ማሳየት።

👉 የአእምሮ እና የአካል ብቃት (Well-being)፦ በስፖርት አማካኝነት የወጣቶችን ሁለንተናዊ ጤና እና የመቋቋም አቅም ማሳደግ።

የዕለቱ የክብር እንግዶች በማጠቃለያው መርሃ ግብር ላይ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሚዲያ አካላት እና የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው ወጣቶቹን አበረታተዋል። በዕለቱ ከተገኙት መካከል አቶ አንዱአለም ጌታቸው (የአዲስ አበባ ኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደር ሎኬሽን ፕሮግራም ዳይሬክተር ) ወ/ሮ ቤቴልሄም ጌታቸው (በኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደር የ Leave No Youth Behind Project ዋና አስተባባሪ) ወጣት ፎሊ ንጉሴ (የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት) እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶች እና ስፖርት እና የሴቶች እና ሕፃናት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል ።

"አንድ ችግኝ ለነገ፣ አንድ አሻራ ለተፈጥሮ"

አረንጓዴ ልማት ከአስደሳቹ የስፖርት ውድድር ጎን ለጎን፣ የ2026 የዓለም የአካባቢ ጥበቃ ቀንን (World Environment Day) በማስመልከት ልዩ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። "አንድ ችግኝ ለነገ፣ አንድ አሻራ ለተፈጥሮ" በሚል መሪ ቃል፤ የተገኙት ወጣቶች፣ የማህበራት አመራሮች፣ የክብር እንግዶች እና የሚዲያ አካላት በጋራ በመሆን የአካባቢ ጥበቃ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ወጣቱ እንደ ስፖርታዊ እንቅስቃሴው ሁሉ ለሀገራዊ አረንጓዴ ልማትም የበኩሉን አሻራ ማሳረፍ እንዳለበት በተግባር አሳይቷል።

በደረጃና የዋንጫ ውጤት በወንዶች እግር ኳስ እና በሴቶች ቮሊቦል Selam Fruits Association እና 4care Leavers Charity Association ያገናኘው የፍጻሜ ጨዋታ ተካሂዶ፡👇

🏆 4care Leavers Charity Association በሁለቱም ፆታዎች የበላይነቱን በመያዝ የተዘጋጀውን ዋንጫዎች ከክብር እንግዶች እጅ ተረክቧል። በሁለተኝነት በሁለቱም ፆታ አሸናፊው selam fruits association ሲሆን 🥉 3ኛ ደረጃ፦ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር (Addis Ababa Youth Association) በሁለቱም ፆታዎች ውድድር ሦስተኛ በመሆን አጠናቋል።

ይህ ልዩ ስፖርታዊ ውድድር በመሆኑ፤ በመድረኩ አሸናፊ እና ተሸናፊ ቢኖርም፣ በዕለቱ የተሳተፋችሁ እና አጋርነታችሁን ያሳያችሁ ሁላችሁም የዚህ ስፖርት ፌስቲቫል አሸናፊዎች ናችሁ!

የላቀ ምስጋና ይህ ታላቅ ስኬት ያለ እናንተ ድጋፍ አይታሰብም ነበርና ልባዊ ምስጋናችንን ለሚከተሉት አካላት እናቀርባለን፡👇

👉 ለክብር ተጋባዥ ቡድናችን ለአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አመራሮች

👉 ለኤስ ኦ ኤስ የህፃናት መንደር አዲስ አበባ ሎኬሽን እና ለ Leave No Youth Behind Project

👉 ለወረዳ 6 የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ

👉 ለከፍተኛ 23 ትምህርት ቤት (የቀድሞው የ SOS ትምህርት ቤት) አጠቃላይ አስተዳደር

👉 ለሁሉም ተሳታፊ ማህበራት፣ የሚዲያ አካላት እና ደጋፊዎች!



SOS Children's Villages in Ethiopia SOS Børnebyerne Embassy of Denmark in Ethiopia የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association SOS Children's Villages International

14/06/2026
14/06/2026
📣 The Grand Finale Match Fixtures Are Out! Who Will Take The Trophy?🔥The stage is set, and the excitement is at its peak...
13/06/2026

📣 The Grand Finale Match Fixtures Are Out! Who Will Take The Trophy?🔥

The stage is set, and the excitement is at its peak! After two weeks of intense competition under the theme “Forward Together - Leave No Youth Behind,” the 1st Care Leavers Associations Sport Festival reaches its historic conclusion this Sunday, June 14, 2026.

Here is the official match schedule for the ultimate showdown:👇

⚽ Men's Football

✅️ 3rd Place Match: 👇

SOS Alumni Youth Association Ethiopia 🆚 Addis Ababa Youth Association

✅️ Grand Finale (🏆 Championship):👇

Selam Fruits Association 🆚 4Care Leavers Charity Association

🏐 Women's Volleyball

(Based on the results of Saturday, June 13, match between Selam Fruits and Addis Ababa)

✅️ 3rd Place Match: (Loser of Saturday's Match) 🆚 SOS Alumni Youth Association Ethiopia

✅️ Grand Finale (🏆 Championship): (Winner of Saturday's Match) 🆚 4Care Leavers Charity Association

🔥 More Than Just a Game — A Celebration of Resilience! This is a unique movement where our youth raise their voices, display their unbreakable unity, and showcase their strength to the entire community.

📍Come out in numbers, cheer for your team, and show your solidarity!

📅 Date: Sunday, June 14, 2026

⏰ Time: Starting from 8:00 AM (Morning)

📍 Venue: Higher 23 Secondary School (Formerly SOS School) — Around Bisrate Gabriel, opposite Adot Cinema.



SOS Children's Villages in Ethiopia SOS Børnebyerne Embassy of Denmark in Ethiopia SOS Children's Villages International SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs Addis Ababa City Administration Bureau Of Women, Children and Social Affair

ከስፖርትም በላይ የሆነው ታላቅ የቤተሰብ በዓል — ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! "Forward Together - Leave No Youth Behind" በሚል መሪ ቃል ላለፉት ሁለት ሳምንታት በደመቀ ...
12/06/2026

ከስፖርትም በላይ የሆነው ታላቅ የቤተሰብ በዓል — ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!

"Forward Together - Leave No Youth Behind" በሚል መሪ ቃል ላለፉት ሁለት ሳምንታት በደመቀ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየው፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የታሪካዊው የCare Leavers Associations Sport Festival ማጠናቀቂያ እና የፍፃሜ ውድድር የፊታችን #እሁድ ይካሄዳል።

ይህ ፌስቲቫል ስፖርታዊ ውድድር ብቻ አይደለም፤ በተለያዩ ተቋማት አድገው ዛሬ ላይ በተለያዩ የህይወት ደረጃ ላይ የሚገኙ ወጣቶች እርስ በእርስ የሚገናኙበት፣ አንድነታቸውን እና ጥንካሬያቸውን ለቀረው ማህበረሰብ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚያሳዩበት ልዩ መድረክ ነው።
ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋማት የስራ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ክቡራን እንግዶች በሚታደሙበት በዚህ ታላቅ ዕለት፤ እርስዎም ተገኝተው ለወጣቶቻችን ያለዎትን ድጋፍ እና አጋርነት እንዲያሳዩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዝዎታለን።

📅 ቀን፦ እሁድ፣ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም (June 14, 2026)

🧭 ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ

📍 ቦታ፦ ከፍተኛ 23 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (የቀድሞው SOS ትምህርት ቤት) — ብስራተ ገብርኤል አካባቢ፣ ከአዶት ሲኒማ ፊት ለፊት።

👉 ኑ! አብረን እንሁን፣ ለወጣቶቻችን ያለንን አጋርነት እና ድጋፍ በጋራ እናሳይ!

# # # # # # # # # # # # # # # # # # # #

🏆 More Than Just a Game: A Grand Family Celebration – You Are Invited!

The historic, first-ever Care Leavers Associations Sports Festival is reaching its grand finale this coming Sunday! For the past two weeks, this vibrant event has been rocking the community under the powerful theme: "Forward Together - Leave No Youth Behind."

This festival is so much more than a sports competition. It is a unique and uplifting platform where youth who grew up in various alternative care structures—now thriving at different stages of life—reunite, celebrate their shared bonds, and amplify their voices of resilience to the wider community. 🗣️✨

🌟 Join Us for the Grand Finale
We are honored to host senior government officials, institutional leaders, and distinguished guests on this momentous day. We warmly invite YOU to join us, stand in solidarity, and show your unwavering support for our incredible youth.

📅 Date: Sunday, June 14, 2026 (ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም)

⏰ Time: Starting from 8:00 AM (ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ)

📍 Location: Keftegna 23 Secondary School (Former SOS School) — Around Bisrate Gabriel, opposite Adot Cinema.

🤝 Come, let’s stand together and show our youth that they have a community that believes in them! See you there!



SOS Children's Villages in Ethiopia SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa የቀድሞ ኤስ .ኦ . ኤስ ወጣቶች ማህበር ኢትዮጲያ / SOS Almuni Youth Association Ethiopia SOS Børnebyerne SOS Children's Villages International SELAM Fruits Association የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs Embassy of Denmark in Ethiopia የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association

ታላቅ የምስራች ለወጣቶቻችን! የአቅም ግንባታ እና የስልጠና እድል ስምምነት🔥ጥምረታችን National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia  ከታዋቂው LG ...
11/06/2026

ታላቅ የምስራች ለወጣቶቻችን! የአቅም ግንባታ እና የስልጠና እድል ስምምነት🔥

ጥምረታችን National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia ከታዋቂው LG KOICA Hope TVET College ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በይፋ መፈራረሙን በደስታ እንገልጻለን ። ይህ ስምምነት ለወጣቶቻችን አዳዲስ የስራ እና የስልጠና በሮችን የሚከፍት ትልቅ እርምጃ ነው ።

📌 የትብብሩ ዋና ዋና የትኩረት መስኮች

ይህ ስምምነት ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን፣ በዋናነት በሚከተሉት የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፡

✅️ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና (TVET)፡ ለብቁ ወጣቶች ደረጃ III እና IV (Level III/IV) የሙያ ስልጠናዎችን ማመቻቸት ።

✅️ የአቅም ግንባታ እና የልምድ ልውውጥ፡ በአሰልጣኞች እና በባለሙያዎች መካከል የክህሎት እና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር የቴክኒክ ትስስር መፍጠር ።

✅️ የስራ ዕድል ፈጠራ ትስስር፡ በኮሌጁ እና በጥምረቱ በኩል የሚገኙ የሥራ ዕድሎችን በጋራ ማስተሳሰር እና ለምሩቃን ሰልጣኞች ማመቻቸት ።

✅️ የጋራ ጥናትና ወርክሾፖች፡ በጋራ የምርምር ሥራዎች፣ ወርክሾፖች እና በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ በጋራ መሥራት ።

💡ስምምነቱ ለወጣቶቻችን ያለው ፋይዳ

ይህ ስምምነት ለአባላትና ለወጣቶቻችን ሰፊ መጻኢ ዕድሎችን ይዞ መጥቷል👇

👉 ጥራት ያለው ትምህርት፡ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እና የገበያውን ፍላጎት ያማከለ የደረጃ III እና IV ስልጠናዎችን በነጻነት የማግኘት ዕድል ።

👉 የስራ ዝግጁነት እና ቅጥር፡ ከስልጠና በኋላ ወደ ሥራው ዓለም ለመግባት የሚያስችሉ የቅጥር ትስስሮች፣ የቃለ-መጠይቅ ዝግጅቶች እና የአቅም ግንባታ ድጋፎች ።
👉 የተሻለ ተወዳዳሪነት፡ ወጣቶቻችን በሀገሪቱ የሥራ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያላቸው እና የወደፊት መሪዎች እንዲሆኑ የላቀ አቅም ይፈጥርላቸዋል ።

♻️ጥምረቱን ወክለው የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የጥምረቱ የቦርድ ፕሬዚዳንት አቶ እዮብ በቀለ ስምምነቱን አስመልክተው የሚከተለውን ብለዋል፦

"ይህ የተደረገው ስምምነት በአማራጭ ህፃናት እንክብካቤ እና ድጋፍ መስጫ ተቋም አድገው ለወጡ ወጣቶች የሙያ እና የክህሎት ስልጠናዎች እንዲያገኙ፣ ከዛም ወደ ስራ አለም እንዲቀላቀሉ እና የተሻለ ዜጋ እንዲሆኑ ያግዛል። ትልቅ ክፍተት በሚታይበት ቦታ ላይ ይህን አይነት እድሎች ለወጣቶቹ ማመቻቸት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ ስምምነቱ እጅግ ጠቃሚ ታላቅ ተግባር ነው።"

ፕሬዚዳንቱ አክለውም ስምምነቱን መሬት ላይ አውርዶ በፍጥነት ወደ ተግባር ለመግባት ሁለቱም ተፈራራሚ አካላት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገልጸዋል። በመጨረሻም ለ LG-KOICA Hope TVET College በ NCLACE ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን🙏 አቅርበዋል።

🔰ይህ ስምምነት ወጣቶቻችን በንድፈ-ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባር የተደገፈ ጥራት ያለው ስልጠና አግኝተው ለስራ ገበያው ብቁ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል ። በተለይም የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎችን (TVET) በነጻነትና በልዩ ትኩረት በማግኘት ፣ የነገውን ተወዳዳሪ እና የወደፊት ህይወታቸውን በራሳቸው መምራት የሚችሉ ዜጎች እንዲሆኑ ትልቅ አቅም ይፈጥርላቸዋል ።

📌ዝርዝር የቅበላ መስፈርቶችን እና መርሃ - ግብሮችን በቅርቡ የምናሳውቅ በመሆኑ ገፃችንን መከታተልዎን ይቀጥሉ።

# # # # # # # # # # # # # # # # # # # #

🎉 Big News for Our Youth! Partnership for Capacity Building and Training Opportunities! 🚀

We are thrilled to officially announce that the National Care Leavers Association Coalition (NCLACE) has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the prestigious LG-KOICA Hope TVET College. This landmark agreement is a massive step forward in opening new doors of employment and skill-training for our youth! 🌟

📌 Key Areas of Collaboration
This partnership will span the next 3 years, focusing on these core pillars:

✅️ TVET Training: Providing Level III and IV vocational training opportunities for eligible youth.

✅️ Capacity Building & Knowledge Sharing: Creating technical networks for skill and knowledge transfer between trainers and experts.

✅️ Job Placement & Linkages: Collaborating on employment opportunities and career readiness training for graduates.

✅️ Joint Research & Workshops: Working together on research projects, workshops, and community service initiatives.

💡 What This Means for Our Care leavers: This agreement brings incredible opportunities directly to our community:👇

👉 Quality Education: Free access to modern, market-driven Level III & IV training backed by advanced technology.

👉 Workforce Readiness: Job placement linkages, interview prep, and career capacity building to ease the transition into the professional world.

👉 Competitive Edge: Empowering our youth to become highly skilled, competitive professionals and future leaders in the job market.

👉Representing the Coalition, Board President Mr. Eyob Bekele shared his thoughts on the impact of this partnership:

"This agreement will greatly assist youth raised in alternative child care institutions by equipping them with professional and vocational skills, helping them transition into the workforce, and enabling them to become exemplary citizens. Bridging this critical gap by providing such opportunities is vital, making this partnership a truly significant milestone." The President expressed full confidence that both parties will swiftly fulfill their responsibilities to turn this agreement into action. He concluded by extending his deepest gratitude to LG-KOICA Hope TVET College on behalf of NCLACE.

🔰 This partnership ensures that our youth receive high-quality, practical training rather than just theoretical knowledge. By prioritizing access to technical and vocational training (TVET), we are empowering the next generation to take control of their futures and become independent, competitive citizens.

📌 Stay tuned! Detailed admission criteria and application schedules will be announced very soon. Keep following our page for updates! 🔔



SOS Children's Villages in Ethiopia SELAM Fruits Association Embassy of Denmark in Ethiopia SOS Børnebyerne SOS Children's Villages International የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa የቀድሞ ኤስ .ኦ . ኤስ ወጣቶች ማህበር ኢትዮጲያ / SOS Almuni Youth Association Ethiopia

📌 ሀገር አቀፍ ተደራሽነትን የማስፋት ጉዞ፡ በኦሮሚያ ክልል የተካሄደ የውይይት መድረክNational Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) ሀገ...
11/06/2026

📌 ሀገር አቀፍ ተደራሽነትን የማስፋት ጉዞ፡ በኦሮሚያ ክልል የተካሄደ የውይይት መድረክ

National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) ሀገር አቀፍ ተደራሽነቱን ለማስፋትና በክልል ደረጃ የሚገኙ ከአማራጭ ክብካቤ እና ድጋፍ መስጫ ተቋማት የወጡ ወጣቶችን ለመደገፍ የጀመረውን ጉዞ ቀጥሏል። በዚሁ መሠረት፣ ግንቦት 27 / 2018 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የተለያዩ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው አጋር ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት ስኬታማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

👉የመድረኩ ዋና ዋና ትኩረቶች፡👇

🔹 በአማራጭ እንክብካቤ እና ድጋፍ መስጫ ተቋማት አድገው የወጡ ወጣቶች የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ተግዳሮቶች መለየትና ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ መወያየት።

🔹 የጥምረቱን (NCLACE) ራዕይ፣ ተልዕኮ እና በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና ስራዎችን ለባለድርሻ አካላት ማስተዋወቅ።

ጥምረቱ በዘንድሮው የበጀት ዓመት በሦስት ክልሎች ላይ ለመድረስ ካቀደው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ውስጥ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ካካሄደው መድረክ ቀጥሎ፣ ይህ በኦሮሚያ ክልል የተደረገው ሁለተኛውና የመጀመሪያው ይፋዊ የትውውቅ መድረክ ነው።

በቀጣይም ግንኙነቱን ይበልጥ በማጠናከር የጋራ ስምምነት ሰነድ (MoU) ለመፈራረም እና ተቀራርቦ ለመስራት በሁለቱም ወገኖች ሙሉ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ለተግባራዊነቱ እና ለዕቅዳችን መሳካት አብራችሁን ለቆማችሁ አጋሮቻችን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን!

# # # # # # # # # # # # # # # # # # # # #

On June 4, 2026, the National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia (NCLACE) conducted a high-level advocacy and consultative forum in the Oromia region. The session brought together key leadership from the Oromia Region Youth and Sports Bureau, along with representatives from various esteemed partner organizations.

Key highlights of the forum included:👇

🔹 Addressing the critical challenges faced by care leavers transitioning from alternative care structures and brainstorming sustainable solutions.

🔹 Introducing the core mission, vision, and strategic ongoing initiatives of NCLACE to regional stakeholders.

As part of our strategic goal to expand regional footprints in three target regions this budget year—following our successful engagement with the Sidama Regional State Women, Children, and Social Affairs Bureau—this milestone meeting marks our initial institutional entry into the Oromia region.

Moving forward, both parties have successfully agreed to institutionalize this partnership and sign a formal Memorandum of Understanding (MoU) in the near future. Together, we are building stronger support systems for our youth.

We extend our deepest gratitude to all regional leadership and development partners who joined us in creating a more supportive environment for care leavers.



SOS Children's Villages in Ethiopia SOS Children's Villages Eastern and Southern Africa የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs SOS Børnebyerne Embassy of Denmark in Ethiopia

09/06/2026

Address

Addis Abeba

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when National Care Leaver's Associations Coalition Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share